Skip to main content
SearchLoginLogin or Signup

ተመራማሪዎች ለተሻሉ ክትባቶች የአፍሪካን ስትሬፕቶኮከስ ዓይነቶችን ይለያሉ።

Amharic translation of DOI: 10.1128/mSphere.00429-20

Published onMay 20, 2023
ተመራማሪዎች ለተሻሉ ክትባቶች የአፍሪካን ስትሬፕቶኮከስ ዓይነቶችን ይለያሉ።
·

የክትባት አዘገጃጀት ሂደትን ለማገዝ በአፍሪካ ውስጥ የስትሬፕ ኤ ኤም ስብስቦች ስርጭት ስልታዊ ግምገማ እና ሜታ-ትንተና ፡፡

የጀርባ ታሪክ:

 የቡድን ኤ ስትሬፕቶኮከስ (ስትሬፕ ኤ) ስነ-ወረርሺኛዊ ክትትል፣ የኤም ፕሮቲን ተግባር እና የክትባት ዝግጅት ስትራቴጂዎች የወደፊት ጥናቶችን ለማመቻቸት እና ለማሻሻል ኤም ስብስብን መሰረት ያደረገ ስርዓት እንደ መደበኛ የመተየብ ዕቅድ ቀርቧል።

በአፍሪካ ለስትሬፕ ኤ ኤም ማስረጃ-ተኮር ስርጭት የምናቀርብ ሲሆን በ ኤም ኤም ስብስብ ዘዴ በመጠቀም አዲሱን የ 30-ቫለንት ክትባት እምቅ ሽፋን እንገመግማለን፡፡

ስልቶች:

 ሁለት ገምጋሚዎች ከአጠቃላይ ፍለጋ የተገኙ ጥናቶችን በየራሳቸው ገምግመዋል ፣ ተዛማጅ መረጃዎችንም አውጥተዋል።

የኤም ስብስቦች ስርጭት ግምቶችን ለማጠቃለል ሜታ-ትንተናዎች (የዘፈቀደ ተጽዕኖዎች ሞዴል) ተካሂደዋል።

ውጤቶች:

 ስምንት ጥናቶች (ቁ=1,595 ገለልተኞች) እንዳሳዩት ዋናዎቹ የኤም ስብስቦች ፡ E6 (18%፣ 95% የመተማመን ክፍተት (መ.ክ)፣ 12.6፤ 24.0%)፣ በማስከተል E3 (14%፣ 95%መ.ክ፣ 11.2፤ 17.4%) እና E4 (13%, 95%CI, 9.5; 16.0%).

በአህጉሪቱ ውስጥ ያሉ ክልሎች የእድሜ እና ማህበራዊ-ኢኮኖሚያዊ ሁኔታዎችን በተመለከተ በኤም ስብስቦች ውስጥ ኢምንት ልዩነት አለ።

የኤም ስብስብ- ተኮር የክትባት ስልትን በተመለከተ በስብስቦች ውስጥ ተሻጋሪ-ጥበቃ እንዳለ ይገመታል፡፡ በአሁኑ ጊዜ በክሊኒክ በመሰራት ላይ ያለው የ 30-ቫለንት ክትባት በአፍሪካ 80.3% ለሚሆኑት ገለልተኞች መላምታዊ ሽፋን ይሰጣል ተብሎ ይታሰባል፡፡

መደምደሚያ:

 ይህ ስልታዊ ግምገማ የሚያመለክተው በአፍሪካ ውስጥ ከፍተኛውን የስትሬፕ ኤ ኤም ስብስብ E6 ሲሆን በቀጣይነት ደግሞ E3፣ E4 እና D4 ይገኛሉ።

የአሁኑ 30- ቫለንት ክትባት በአፍሪካ ውስጥ ተነሰራፍተው ላሉት የተለያዩ የኤም ስብስብ አይነቶች ከፍተኛ ሽፋን ይሰጣል፡፡

የወደፊት ጥረቶች አዲሱ የ30- ቫለንት ክትባት እምቅ ሽፋን ምን ያህል እንደሆነ መገመት ላይ ሊያተኩሩ ይችላሉ፤ ይህም የሚመሰረተው በ ተሸጋሪ-የማመቻቸት ጥናቶች ላይ ሲሆን ለስትሬፕ ኤ በሽታዎች በጣም ተጋላጭ ከሆኑት ህዝቦች መሃል ተወካይ የ ስትሬፕ ኤ ገለልተኞችን በማጥናት ይካሄዳል፡፡

አስፈላጊነት፡

 በተለይም ብዙ ጊዜ የስነ-ወረርሺኛዊ መረጃዎች በማይገኙባቸው እና በማደግ ላይ ባሉ ሃገሮች፣ ዝቅተኛ የክትባት ሽፋን የህብረተሰቡን ጤና አስመልክቶ እጅግ አሳሳቢ ጉዳይ ነው፡፡

ስትሬፕቶኮከስ (ስትሬፕ ኤ) ለማሳወቅ ከአፍሪካ የስትሬፕ ኤ ስበስብ ኢንፌክሽኖች ስለ ኤሜ ፕሮቲን ኤም ኤፒዲሚዮሎጂ እንዘግባለን፤ በአነዚህ ቦታዎች ከስትሬፕ ኤ ጋር የተያያዙ በሽታዎች እና ውርዴዎቻቸው ሩማቲክ ትኩሳት እና ሩማቲክ ልብ ህመምን ጨምሮ ሃይለኛ ሸክም ናቸው፡፡

ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ በአፍሪካ ዙሪያ ስለ ኤም ስብስቦች የቀረበው ዘገባ አሁን በሙካራ ላይ ያለው ኤም ፕሮቲን ክትባት ከፍተኛ ሽፋን የመኖር እድል እንዳለው ይጠቁማል፤ ለዚህም የኤም-ስብስብ ተኮር ዘዴ ጥቅም ላይ ይውላል፡፡


ተመራማሪዎች ለተሻሉ ክትባቶች የአፍሪካን ስትሬፕቶኮከስ ዓይነቶችን ይለያሉ።

 በስትሬፕቶኮከስ ባክቴሪያ ላይ ብዙ ጥናቶችን ከተመለከቱ በኋላ ተመራማሪዎች በአፍሪካ የተለመዱትን ዓይነቶች ለይተዋል።

ግኝቶቻቸው ከተወሰኑ ዓይነቶች ወደ የተሻሉ ክትባቶች የሚደረገውን ምርምር ያሳድጋል።

 የቡድን ኤ ስትሬፕቶኮከስ ባክቴሪያ ወይም ‘GAS’ ኢንፌክሽን፣ የሳንባ ምች እና የመርዛማ ክውታ ሲንድሮምን ጨምሮ ለብዙ ከባድ ህመሞች ሊዳርግ እና ገዳይ ሊሆንም ይችላል።

በአፍሪካ በየዓመቱ 1.78 ሚሊዮን ከባድ የ GAS ክስተቶች ይከሰታሉ።

 ከ200 በላይ የGAS ዝርያዎች ወይም “ዓይነቶች” ተለይተዋል፤ ስለዚህ ሳይንቲስቶች ኤም ፕሮቲን በተባለው ልዩ ፕሮቲን አማካኝነት በሚመጡ ልዩነቶች ላይ ተመርኩዘው በቡደን የማስቀመጥ ስርዓትን ፈጥረዋል።

ይህን አካሄድ በመጠቀም ኤም ስብስቦች የተባሉትን ተመሳሳይ ዓይነት ቡድኖችን ዒላማ ያደረገ ክትባት ፈጥረዋል።

ክትባቱ ባደጉት ሃገራት ከተደረጉት ጥናቶች በተገኙ መረጃዎች ላይ የተመሰረተ ነው፤ ነገር ግን በአፍሪካ ምን ያህል ጠቃሚ ሊሆን እንደሚችል ብዙ መረጃ የለም።

 በዚህ ጥናት ውስጥ ተመራማሪዎች በአህጉሪቱ ውስጥ የትኞቹ የኤም ስብስቦች በጣም የተለመዱ እንደሆኑ ለማወቅ ከሌሎች የአፍሪካ ሃገራት GAS ጥናቶች የተገኘውን መረጃ አወዳድረዋል።

በተለይም አሁን ያለው ክትባት በክልሉ ውስጥ ምን ያህል ውጤታማ ሊሆን እንደሚችል ለመረዳት ፈልገዋል።

 ተመራማሪዎቹ በአፍሪካ ሰፋ ያሉ ሳይንሳዊ መጣጥፎችን ስለ GAS በመፈለግ የጀመሩ ሲሆን ግኝቶቻቸውን በተለይ ኤም ስብስቦች ላይ ወደሚያተኩሩት ጠበብ አድርገው ነበር።

ይህም በአጠቃላይ ከአምስት ሃገሮች ከተገኙ ስምንት ጥናቶች ጋር አስቀርቷቸዋል:

ደቡብ አፍሪካ፣ ማሊ፣ ኬንያ፣ ታንዛኒያ እና ቱኒዚያ።

 እነዚያን ጥናቶች በበለጠ ዝርዝር በመተንተን ተመራማሪዎቹ የትኞቹ የኤም ስብስቦች በጣም የተለመዱ እንደሆኑ እና ምን ያህል ነጠላ የGAS ዓይነቶች እንደተገኙ ማወቅ ችለዋል።

ከዚያም ያንን መረጃ አዲስ የተዘጋጀው ክትባት ዒላማ ካደረጋቸው ልዩ የGAS ዓይነቶች ጋር አነጻጽረውታል።

በአህጉሪቱ ውስጥ የሚታዩ አራት የተለመዱ ስብስቦችን አግኝተዋል ነገር ግን በእነሱ የተጠቁ ሰዎች ዕድሜ ወይም ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ሁኔታ ላይ ብዙ ልዩነት አላዩም።

 በአፍሪካ ውስጥ የተከሰቱትን የGAS ዓይነቶች ክትባቱ ከሚከላከለው አይነት ጋር ሲያወዳድሩ ክትባቱ ወደ 60% ለሚሆኑት ዓይነቶች ውጤታማ ሊሆን እንደሚችል ተገንዝበዋል።

ነገር ግን ተመራማሪዎቹ ክትባቱ ከተመሳሳይ የኤም ስብስቦች አካል ከሆኑ ዓይነቶች የተሻለ ሊከላከል እንደሚችል ጠቁመዋል።

ይህ ማለት በተግባር ክትባቱ ሰዎችን በአፍሪካ ውስጥ ከሚገኙ 80% የGAS ዓይነቶች ይከላከላል ማለት ነው።

 ግኝቶቹ እንደሚያሳዩት አዲሱ የGAS ክትባት በአፍሪካ ውጤታማ ሊሆን ይችላል ነገር ግን ተመራማሪዎቹ የተለመደው የአፍሪካ ኤም ስብስብ በሌሎች በርካታ የዓለም ክፍሎች ከሚታየው ጋር ተመሳሳይ እንዳልሆነ ይጠቁማሉ።

ለወደፊቱ ክትባቶች በሚመረቱበት ጊዜ በበቂ ሁኔታ ያልተወከሉ ዓይነቶችን መጨመር በአፍሪካ አውድ የበለጠ ውጤታማ ያደርጋቸዋል።

 ተመራማሪዎቹ በብዙ ዝቅተኛ እና መካከለኛ ገቢ ባላቸው የአፍሪካ ሃገራት ስለ GAS የመረጃ እጥረት መኖሩንም ጠቅሰዋል።

ከእነዚህ አካባቢዎች መረጃ መጨመር ለሳይንቲስቶች ስለ ችግሩ የበለጠ ዝርዝር መግለጫ ሊሰጣቸው ይችላል።

 በተጨማሪም ምናልባት አዳዲስ ዝርያዎች ስለሆኑ የኤም ስብስብ ስርዓት አካል ያልሆኑ አንዳንድ የGAS ዓይነቶች አሉ።

እነዚህ ዓይነቶች የት እንደሚገቡ በማወቅ ላይ ያተኮረ የወደፊት ጥናት ለተሻለ የክትባት ግኝት እና በአፍሪካ ለታካሚዎች የተሻለ ውጤትን ያስገኛል።

 ጥናቱ በአፍሪካ አውድ ውስጥ ለወደፊት ስራ አስፈላጊ ዘርፎችን አጉልቶ ያሳያል፤ እና ለአህጉሪቱ ስለ GAS ኤም ስብስቦች የመጀመሪያው ጥናት ነው።

ስራው በደቡብ አፍሪካ እና በአሜሪካ ተመራማሪዎች መካከል በትብብር የተሰራ ነው።

Connections
1 of 5
Comments
0
comment
No comments here
Why not start the discussion?